የሰሜን ሸዋ ዞን ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት መምሪያ 2018 በጀት የ1ኛ ሩብ ዓመት የስራ አፈፃፀም ገምግሟል ። በስራ ቡድኖች ሪፖርት የቀረበ ሲሆን ከፍተኛ አፈፃፀም መመዝገቡም ተመላክቷል ። የቀጣይ ጊዚያት ተግባራትን እና የማስፈፀሚያ ስልቶችም ለውይይት የቀረቡ ሲሆን የመምሪየው ሀላፊ አቶ ደምሰው መንበሩ ከዚህ የበለጠ ለመስራት ሁሉም ፈፃሚ በየስራ ድርሻው የተቀመጠውን የቁልፍ ነጥቦች መለኪያን መሠረት አድርገን መስራት ይገባል ብለዋል ። ከዚህ በተጨማሪ የዞኑን በ2017 በጀት አመት የላቀ አፈፃፀም የነበራቸውለመምሪያው ባለሙያዎች ማበረታቻ ሽልማት እና የእውቅና ሰርተፊኬት ፣ የማኔጅመንት አባላት የዕውቅና ምስክር ወረቀት ከመምሪያው ሀላፊ ከአቶ ደምሰው መንበሩ እጅ ተቀብለዋል ።
በአብክመ የኢንዱሰትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ድጋፍ ቡድን በሰሜ ሸዋ ዞን ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ እና በስሩ ለሚገኙት ቡልጋ ከተማ አስተዳደር እና አንጎለላና ጣራ ወረዳ በመስክ እና በቢሮ በመገኘት ድጋፍ ሰጥቷል ። በዚህ ድጋፍ የዞኑን መምሪያ ወረዳዎችን የሚደግፍበትን እና በአጠቃላይ የድጋፍና ክትትል ስርዓቱን ፤ የዞኑን የቁልፍና አበይት ተግብራት አፈፃፀምን በ2018 አሰከ አሁን ባለው የሰራ እንቅስቃሴ የነበሩ ጠንካራና እና ደካማ ስራዎችን ያመላከቱ ሲሆን በመጨረሻም ሁለተኛው ሩብ አመት አፈፃፀሙ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ የቀጣይ አቅጣጫዎችን በመስቀመጥ ለመግባባት ተችሏል ።
የሰሜን ሸዋ ዞን ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ዙር የባለሃብት ምክክር መድረክ /የኢንቨስትመንት ፎረም/ በአንጎለላናጣራ ወረዳ ጎልባ ቀበሌ የካቲት 2/2017 ዓም ተካሂዷል፡፡ በዚህ መድረክ ላይ የክልል እና የዞን ከፍተኛ አመራሮች ፣ የወረዳ አመራሮች ፣ አጋር አካላት ፣ ባለሃብቶች ፣ የዞን መምሪያ ማኔጅመንት አባላት እና ባለሞያዎች ተገኝዋል፡፡ በዚህ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የተከበሩ አብዱ ሁሴን (ዶክተር)በሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላና ጠራ ወረዳ ጎለባ ቀበሌ የሚገኘውን በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ባጃጆችን የሚያመርት እና የወረቀት ፋብሪካዎችን መርቀዋል። በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የከተሞች ክላስተር አስተባባሪና የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ የተከበሩ አህመድን መሃመድ (ዶክተር)፣ የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዲሪስ አብዱን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች ተገኝተዋል። አመራሮቹ ከምርቃ ሥነ ሥርዓቱ በተጓዳኝ ሌሎች በአንጎለላና ጠራ እና ቡልጋ ከተማ አስተዳደር በማምረት ላይ የሚገኙ ፋብሪካዎችን በመጎብኘት አበረታተዋል። ከተጎበኙት ፋብሪካዎች መካከል በአንጎለላና ጠራ ወረዳ የሚገኘው ጀር የተቀናጀ የምግብ ማምረቻ፣ ኤቨርብራት የፕላስቲክ ፋብሪካ እና ሌሎችም ይገኙበታል። ጀር የተቀናጀ የምግብ ማምረቻ በአሁኑ ሰዓት ዘይት እያመረተ ሲሆን፣ በቀጣይ ሁለት ወራት አልሚ ምግቦችን ማምረት እንደሚጀምር ተጠቁሟል።በተዘጋጀው መድረክ ላይ የዞኑን የኢንቨስትመንት ሰነድ በዞኑ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ ደምሰው መንበሩ የቀረበ ሲሆን ይህንን ተከትሎ ፓነል ውይይት ተደርጓል፡፡ በፓናል ውይይቱ ላይ በባለሃብቱ የተለያዩ ጥያቄዎች ቀርበው ምላሽ ይተሰጣቸው ሲሆኑ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ምላሸ የሚሰጣቸውም እንዳሉ ተገልጧል ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ግንባታቸውን ጨርሰው ወደ ምርት ለገቡ 10 የአምራች ኢንዱስትሪዎች የሰርተፊኬት እና የክሪሰታል ሽልማት ከክብር እንግዶቹ ተቀብለዋል፡፡ለአጋር አካላትም እንዲሁ ስለነበራቸው መልካም አስተዋጽዖ የሰረተፊኬት ሽልማት ተሰጥቷል፡፡
በሰሜን ሸዋ ዞን ቡልጋ ከተማ ጥር 27/2017 ዓም የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በሚል መሪ ቃል ወረዳዊ የኢንቨትመት ፎረም ተካሄደ፡፡ በመድረኩ የከተማው አስተባባሪ አመራሮቾ፣ጠቅላላ አመራሮች ፣ ባለሀብቶቾ፣ ተጋባዠዥ እንግዶች እና የሁሉም ባንክ አመራሮች በተጨማሪም የከተማው የኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመት ፅ/ቤት ባለሙያዎች በተገኙበት በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል፡፡ በዕለቱም ባለሀብቱ ያለባቸውን ችግር ማለትም የመሠረተ ልማት መብራት ፣ መንገድ እንዲሁም የብድር ፣የጥሬ ዕቃ እና ለከተማው አስተዳደር ነዋሪው ህብረተሰቡን በልማት እና ከስራ ዕድል ፈጠራ አንጻር ከማገዝ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል፡፡
የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ስትሪንግ ኮሚቴ እቅዱን እና ተግባራቶችን ገመገመ።በሰሜን ሸዋ ዞን ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ የኢንቨስትመንቱን ዘርፍ የሚያነቃቃውን የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ሁነት የካቲት 2/2017 ዓ.ም በዞኑ አንጎለላና ጠራ ወረዳ ማካሄዱን ተከትሎ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።በዛሬው እለትም ሁሉም የዞን መምሪያ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ዘርፉ ያለበትን ሁኔታ ግምገማ ተደርጓል።የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ተክለየስ በለጠ እና የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አይነኩሉ አበበ መድረኩን መርተውታል።የመምሪያው ሃላፊ አቶ ደምሰው መንበሩ መነሻ ሃሳብ አቅርበዋል ውይይትም ተደርጎበታል። የቀጣይ አቅጣጫዎችም ተመላክተዋል- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ መድረክ ተቋማዊ ሆኖ እንዲመራ ማድረግ እንዳለበት - 5ቱ የክላስተር አስተባባሪዎች በስራቸው ያሉትን ኮሚቴዎች እቅድ አቅደው እንዲወያዩ አቅጣጫ ተቀምጧል- የኢትዮጵያ ታምርት የንቅናቄ መድረኩን በድምቀት ለማክበር ሁሉም የክላስተር አስተባባሪ በባለቤትነት በመያዝ በአሉን በድምቀት ለማክበር የድርሻውን መወጣት እንዳለበት መግባባት ተፈጥሯል።በየደረጃ ያለ አመራር የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ መድረክ ላይ ባለሀብቶች እንዲሳተፉ የተጠናከረ ስራ መሰራት እንዳለበት መግባባት ላይ ተደርሷል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ስትሪንግ ኮሚቴ እቅዱን እና ተግባራቶችን ገመገመ።በሰሜን ሸዋ ዞን ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ የኢንቨስትመንቱን ዘርፍ የሚያነቃቃውን የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ሁነት የካቲት 2/2017 ዓ.ም በዞኑ አንጎለላና ጠራ ወረዳ ማካሄዱን ተከትሎ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።በዛሬው እለትም ሁሉም የዞን መምሪያ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ዘርፉ ያለበትን ሁኔታ ግምገማ ተደርጓል።የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ተክለየስ በለጠ እና የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አይነኩሉ አበበ መድረኩን መርተውታል።የመምሪያው ሃላፊ አቶ ደምሰው መንበሩ መነሻ ሃሳብ አቅርበዋል ውይይትም ተደርጎበታል። የቀጣይ አቅጣጫዎችም ተመላክተዋል- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ መድረክ ተቋማዊ ሆኖ እንዲመራ ማድረግ እንዳለበት - 5ቱ የክላስተር አስተባባሪዎች በስራቸው ያሉትን ኮሚቴዎች እቅድ አቅደው እንዲወያዩ አቅጣጫ ተቀምጧል- የኢትዮጵያ ታምርት የንቅናቄ መድረኩን በድምቀት ለማክበር ሁሉም የክላስተር አስተባባሪ በባለቤትነት በመያዝ በአሉን በድምቀት ለማክበር የድርሻውን መወጣት እንዳለበት መግባባት ተፈጥሯል።- በየደረጃ ያለ አመራር የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ መድረክ ላይ ባለሀብቶች እንዲሳተፉ የተጠናከረ ስራ መሰራት እንዳለበት መግባባት ላይ ተደርሷል።
በሰሜን ሸዋ ዞን ቡልጋ ከተማ ጥር 27/2017 ዓም የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በሚል መሪ ቃል ወረዳዊ የኢንቨትመት ፎረም ተካሄደ፡፡ በመድረኩ የከተማው አስተባባሪ አመራሮቾ፣ጠቅላላ አመራሮች ፣ ባለሀብቶቾ፣ ተጋባዠዥ እንግዶች እና የሁሉም ባንክ አመራሮች በተጨማሪም የከተማው የኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመት ፅ/ቤት ባለሙያዎች በተገኙበት በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል፡፡ በዕለቱም ባለሀብቱ ያለባቸውን ችግር ማለትም የመሠረተ ልማት መብራት ፣ መንገድ እንዲሁም የብድር ፣የጥሬ ዕቃ እና ለከተማው አስተዳደር ነዋሪው ህብረተሰቡን በልማት እና ከስራ ዕድል ፈጠራ አንጻር ከማገዝ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል፡፡