የአሳግርት ወረዳ በአማራ ብሔራዊ ክልልዊ መንግስት በሰሜን ሸዋ ዞን መስተዳድር ከሚገኙ 31 ወረዳእና ከተማ አስተዳደሮች ውስጥ አንዷ ስትሆን ወረዳዋ በሰሜንና በሰሜን ምዕራብ አንጎለላና ጠራ ወረዳ ፣ በሰሜንና በሰሜን ምስራቅ አንኮበር ወረዳ ፣ በደቡብ በረኽት ወረዳ ፣ በምዕራብ ሀገረማርያም ከሰም ወረዳ እና በምስራቅ የአፋር ክልል ያዋስኗታል፡፡ወርዳዋ በጠቅላላው የአስራ ሶስት(13) የገጠር ቀበሌና የሁለት ከተሞች ባለቤት ናት፡፡
ወረዳዋ ከሀገሪቱ ርዕሰ ሚዲና ከአዲስ አበባ በሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ በ125 ኪ.ሜ፣ ከክልላችን ርዕሰ መዲና ከባህር ዳር ደግሞ 614 ኪ.ሜ እንዲሁም ከዞናችን ርዕሰ መዲና ደ/ብርሃን ደግሞ በስተደቡብ አቅጣጫ 72 ከ.ሜ ርቀት ላይ የምትገኝ ሲሆን ወረዳዋ ከሰንቦ-አረርቲ-ሞጆ የአስፋልት መንገድ በ26 ከ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡
የሚሸፍኑት የቆዳ ስፋትም ፡-