የሰሜን ሸዋ ዞን ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት መምሪያ ለዞኑ ወረዳዎ እና ከተማ አስተዳደሮች ዕወቅና ሰጠ፡፡
 Office news 
  quarter evaluation 
       Posted by  nszii on 2025-10-31 04:42:54 |
	
          Last Updated by  nszii on 2025-10-31 04:42:54
       
  
              የሰሜን ሸዋ ዞን ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት መምሪያ  ዛሬ መስከረም 12 /2018 ዓም ባደረገው የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ ትውውቅ መድረክ ከዞኑ ካሉት የ ወረዳ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤቶች መካከል 
ተወዳድረው የተሻለ አፈፃፀም ያላቸውን ለይቶ የዋንጫና የሰርተፌኬት ሽልማት ሰጥቷቸዋል ። በዚህም 
1ኛ. ም/ሸንኮራ ወረዳ 
2ኛ . አንጎለላና ጣራ ወረዳ 
3ኛ. መንዝ ጌራ ወረዳ ሲሆኑ  በከተማ አስተዳድር የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት በኩልም በተመሳሳይ 
  1ኛ. ቡልጋ ከተማ አስተዳደር 
 2ኛ. መሐል ሜዳ ከተማ አስተዳደር 
 3ኛ . ደ/ሲና ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት በመሆን ወጥተዋል ። ሽልማታቸውንም ከእለቱ የክብር እንግዶች   ከአብክመ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ ከአቶ ኢንድሪስ አብዱ እና ምክትል ቢሮ ኃላፊ ከአቶ ተፈሪ ታረቀኝ እጅ ተቀብለዋል ።በዕለቱም ከሁሉም የወረዳና ከተሞች የጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር መምሪያው የመግባብያ ሰነድ ተፈራርሟል ።
             Share: Facebook | 
Twitter |
Whatsapp | 
Linkedin  Visits: 17